Get Mystery Box with random crypto!

Remedial Program

Logo des Telegrammkanals remedialprogram_1 - Remedial Program R
Logo des Telegrammkanals remedialprogram_1 - Remedial Program
Adresse des Kanals: @remedialprogram_1
Kategorien: Uncategorized
Sprache: Deutsch
Abonnenten: 565

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


Die neuesten Nachrichten

2023-03-01 21:43:35
በ2015ዓ.ም የት/ት ዘመን በጅማ ዩኒቨርስቲ ለተመደባችሁ አዲስ ገቢ የቅድመ ምረቃ መደበኛ እና Remedial ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ ምዝገባችሁ:
የካቲት  29 እና 30/2015ዓ.ም እንደሚካሄድ ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
1.1K viewsedited  18:43
Öffnen / Wie
2023-03-01 15:57:09
በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ ለማካካሻ ትምህርት ፕሮግራም የተመደባቹህ ተማሪዎች የግቢ መግቢያ ጊዜ መጋቢት 01-02/2015 መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።


ተጨማሪ መረጃ ከምስሉ ይመልከቱ

https://t.me/Remedialprogram_1
 https://t.me/Remedialprogram_1
1.0K viewsedited  12:57
Öffnen / Wie
2023-03-01 14:46:52
የ2015 ዓ/ም ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ውጤት ይፋ ሆኗል።

በዚህ አመት የተዘጋጀው መቁረጨ ነጥብ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎችን ታሳቢ ተደርጎ የተሰላ በመሆኑ የሚያገለግለው ለ2015 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ብቻ መሆኑን ተገልጿል።

በ2013/2014 የሥልጠና ዘመን በተለየየ ምክንያት ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት ያልገቡ ተማሪዎች የሚስተናገዱት በ2014 ዓ.ም በነበረው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ይሆናል ተብሏል።

(የ2015 ዓ/ም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ውጤት ከላይ ተያይዟል)

ምንጭ፦ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
887 views11:46
Öffnen / Wie
2023-02-28 19:51:24
#Update #UAE

በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተማሪዎቹ " እንኳን ደስ ያላችሁ " ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው " ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡

ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ  አሳስበዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል፤ በተለይ " ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ  " ብለዋል።

#ኤፍቢሲ

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
842 viewsedited  16:51
Öffnen / Wie
2023-02-28 13:35:29
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ መደበኛ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው በ2015 ዓ.ም በመደበኛ መርሃ ግብር የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ከየካቲት 20 እስከ 22/2015 ዓ.ም እንደሆነ መግለጹ ይታወቃል።

መንግስት ዘንድሮ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች
ምደባ ካደረገባቸው 15 ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ5 ሺህ 100 በላይ ተማሪዎች በቀዳሚነት የመረጡት ዩኒቨርሲቲ ነው።

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
805 views10:35
Öffnen / Wie
2023-02-27 22:17:22
#የጥሪማስታወቂያ
Welkite University For Remedial Students

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
1.1K viewsedited  19:17
Öffnen / Wie
2023-02-27 21:10:29 #Episode2

ግቢ ላይ ውጤት እንዴት መስራት እንችላለን።

         Worksheet

Worsheet ማለት መምህሩ የሆነ chapter አስተምሮ እንደጨረሰ በተማራችሁት ትምህርት ዙሪያ ከበድ ከበድ ያሉ እና የ concept ጥያቄዎች ከተለያዩ መፅሀፍት አውጣጥቶ ፈተና ሊደርስ አካባቢ የሚሰጣችሁ ነው። በተለይ ፈለጣ የሚበዛበት ዲፓርትመንት የምትገቡ ልጆች worksheet የተለመደ ነው። መምህሩ worsheet ከሰጣችሁ ፡  ፈተናውን በዚህ መልክ ተዘጋጁ ማለቱ ነው። ከ worksheet ቱ ላይ ጥቂት የማይባሉ ጥያቄዎች ፈተና ላይ ይወጣሉ። መምህሩ ጥያቄዎቹን የሚያወጣው ከ መፅሀፍ ስለሆነ የጥያቄዎቹን መልስ ከዛው መፅሀፍ ታገኙታላችሁ ፡ ከሌለ ደግሞ Google ማድረግ ይጠበቅባችሗል። ስለዚህ የሚሰጣችሁን worksheet ጥሩ አድርጋችሁ ከሰራችሁ ፡ ፈተናውን ትሰሩታላችሁ።

    የአጠናን መንገድ(ስልት)

እንዴት አድርገን ብናጠና ነው ፡ ግቢ ላይ ውጤት መስራት የምንችለው ?

አንዳንድ መምህሮች ሙሉ chapter ሩን እንድትፅፋ አድርገው ፈተና የሚያወጡ አሉ። ለምሳሌ ፡ List and describe , explain and discuss ምናምን እያለ handout ቱ ላይ ያሉትን ኖቶች እንድትፅፋ አድርጎ የሚያወጣ መምህር አለ።

አንዳንድ መምህሮች ደግሞ የ concept ጥያቄ የሚያወጡ አሉ። የ እናንተን የመረዳት ችሎታ የሚጠይቁ ጥያቄዎችን የሚያወጡ መምህሮች አሉ።

አንዳንድ መምህሮች ደግሞ የ case ጥያቄዎችን ይጠይቃሉ። የ case ጥያቄዎች ደግሞ የእናንተን የመረዳት ፡ የማብራራት ፡ እና ተግባራዊነት የሚጠይቁ ናቸው።

ስለዚህ እንዴት እናብብ

የመጀመሪያው ፈተና ላይ መምህሩ ምን አይነት የፈተና አወጣጥ ስታይል እንዳለው አታውቁም ።

ከመጀመሪያው ፈተና በሗላ ግን የመምህሩን የፈተና አወጣጥ ስታይል ማወቅ ትችላላችሁ። ስለዚህ

የ ሽምደዳ ጥያቄዎችን የሚያወጣ ከሆነ ፡ እናንተም በዛው ልክ handout ቱን በ straw ምጥጥ አድርጋችሁ ማንበብ ነው። በርግጥ ሽምደዳ boring ነው ፡ በተለያየ ስልት አንብባችሁ መያዝ ነው።

  መምህሩ የ concept ጥያቄችን የሚያወጣ ከሆነ ፡ እናንተም በቻላችሁ መጠን የብልጠት አነባበብ መከተል ነው። በቻላችሁት መጠን ሳይንሱን ለመረዳት ብላችሁ አንብቡ።

የ case ጥያቄዎች ከበድ ይላሉ ። ስለዚህ ስታነቡ ፡ የምታነቡት ትምህርት ተግባራዊ እውነታውን ማወቅ ፡ የት የት ቦታ apply እንደሚደረግ ፡ advantage and disadvantage ን ማወቅ ። ከዛ በዚህ መሰረት ማብራራት ነው ከእናንተ የሚጠበቀው።

ስለዚህ የአጠናን ስልታችሁ እንደመምህሩ ፈተና አወጣጥ ቢሆን ብለን እንመክራለን።

     የጊዜ አጠቃቀም

ሌላኛው ና መሰረታዊ ነገር ጊዜያችሁን በአግባቡ የመጠቀም ጉዳይ ነው። ምንድን መሰላችሁ ፡ ብዙዎቻችን ቆይ ነገ አነበዋለሁ ፡ ቆይ ቡሗላ አነበዋለሁ እያልን የመዘናጋት አባዜ አለብን። ይህ ደግሞ የምናነባቸው ትምህርቶች እንዲደራረቡን ያደርጋል። ከ ተደራረቡብን ደግሞ በ tension ልንጨልል እንችላለን። ስለዚህ በተቻለን መጠን ፡ ሳንዘናጋ ፈተናዎች ከመድረሳቸው በፊት ብናነብ መልካም ነው።

      አለመሰልቸት

ግቢ ላይ ፈተናዎች ፡ አሳይመንቶች ፡ ፕሮጀክቶች ይደራረባሉ። በተለይ በቀጣይ ወደ ግቢ የምትገቡ ፍሬሽ ተማሪዎች ፡ ለ እያንዳንዱ ሴሚስተር የሚሰጣችሁ ጊዜ አጭር ነው። በዚህ ምክንያት ፈተና ቶሎ ቶሎ ነው የምትፈተኑት ፡ አሳይመንት ተደራርቦ ነው የሚሰጣችሁ። ምናልባት ዛሬ ተፈትናችሁ ፡ ነገም ሌላ ፈተና ትፈተናላችሁ ። ከፈተና እንደተመለሳችሁ አሳይመንት ልትሰሩ ትችላላችሁ ምናምን። እና ይኸ መደራረብ መሰልቸን ያመጣል። ስለዚህ ፅኑ መሆን ይጠበቅባችሗል።

   ከመምህር ጋር ሰላማዊ መሆን።

ሁሉንም ማለት ባይቻልም የግቢ መምህሮች ባህሪያቸው አስቸጋሪ ነው። በቻላችሁ መጠን ከመምህራኖቻችሁ ጋር ሰላማዊ መሆን ፡ በትህትና መነጋገር ፡ ለመምህሩ የሚመች ክላስ መፍጠር አለባችሁ። ከመምህር ጋር የምትንገራገጩ ከሆነ ግን ፡ ሆን ብሎ ውጤታችን ያወርድባችሗል። ብዙ ገጠመኝ ስለማውቅ ነው በዚህ ጉዳይ።

    Google

ለ ግቢ Google በጣም ወሳኝ ነገር ነው። Assignment መስራት ብትፈልጉ ፡ practical education በ video  ማየት ብትፈልጉ ፡ የተለያዩ መፅሀፎችን እና የመፅሀፍ solution ማውረድ ብትፈልጉ ፡ ምናልባት መምህሩ የሰጣችሁ ኖት ካልገባችሁ እና ሳይንሱን መረዳት ብትፈልጉ ፡ Google ለነዚህ ሁሉ በቂ መፍትሔ አለው። ስለዚህ Google ን የቅርብ ወዳጅ አድርጋችሁ ወጤት መስራት ትችላላችሁ ፡ ሳይንሱን መረዳት ትችላላችሁ። በዚሁ አጋጣሚ ለ Google ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ ።

          The End

 https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
899 viewsedited  18:10
Öffnen / Wie
2023-02-27 21:04:05
#WachemoUniversity

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሬመዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ከየካቲት 21 እስከ 24/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ተቋሙ ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

መሰናዶ ያለፋችሁበት ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒ፣
ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
3×4 ፎቶግራፍ (4)፣
የሌሊት አልባሳትና የስፖርት ትጥቅ።

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
752 viewsedited  18:04
Öffnen / Wie
2023-02-27 14:12:26
#AASTU

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ.ም አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡

በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ካመጡ ተማሪዎች መካከል፤ ከ1 ሺህ 800 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መመደባቸው ይታወቃል።

ዩኒቨርሲቲው በ2015 ዓ.ም የተማሪዎቹ የመግቢያ ጊዜ ዛሬ የካቲት 20/2015 ዓ.ም ብቻ መሆኑን መግለፁ አይዘነጋም።

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
747 viewsedited  11:12
Öffnen / Wie
2023-02-27 12:16:22
#የሥራ_ቅጥር_ዕድል
#አክሱም_ዩኒቨርሲቲ

በአክሱም ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅና ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ
የሙያ መስኮች መምህራንና የጠቅላላ ሐኪሞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

የሥራ መደብ ➭ በተለያዩ የሙያ መስኮች
ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት ➭43
ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ ➭ መጀመሪያ ዲግሪ
የሥራ ቦታ ➭ አክሱም ዩኒቨርሲቲ
የሥራ ልምድ ➭ ዜሮ ዓመት
የማመልከቻ ጊዜ ➭ የካቲት 24/2015 ዓ.ም ያበቃል

አመልካቾች የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒውን በመያዝ በዩኒቨርሲቲው ህክምና ትምህርት ቤት በመቅረብ መመዝገብ ትችላላችሁ።

https://t.me/Remedialprogram_1
https://t.me/Remedialprogram_1
735 viewsedited  09:16
Öffnen / Wie